Virginia ከTexas እና North Carolina በመቀጠል በሀገሪቷ ሶስተኛው ትልቁ በስቴት የሚተዳደር የአውራ ጎዳና ሥርዓት ያላት ሲሆን፣ በኮመንዌልዙ የትራንስፖርት አገልግሎት ቦርድ በኩል ለአየር ማረፊያዎች፣ የባህር ወደቦች፣ ባቡሮች እና የሕዝብ ማመላለሻዎች የገንዘብ ድጋፍ ታቀርባለች።
Virginia 511 የሞባይል ስልክ መተግበሪያ ከVirginia የትራንስፖርት አገልግሎት መምሪያ ለሚገኝ የትራፊክ መረጃ ይፋዊው ምንጭ ነው። ካርታን መሰረት ያደረገው በይነ-ገጽ አሁን እየተከናወኑ ላሉ እና ወደፊት ለታቀዱ የመንገድ ሥራዎች፣ ለወቅታዊ ክስተቶች እና የትራፊክ ፍጥነቶች፣ ለክረምት መንገድ ሁኔታዎች፣ መርሃ ግብር ለተያዘላቸው የድልድይ መክፈቻዎች እና በመላው ስቴት ለሚከናወኑ ሌሎች ዝግጅቶች ተደራሽነትን ያቀርባል። በተጨማሪም የስቴቱን የመንገድ ዳር የትራፊክ ካሜራዎች በመጠቀም ቀጥታ ስርጭት በሚያስተላልፉ ከ 800 በላይ የቪዲዮ ስርጭቶች አሁን ያሉትን የመንገድ ሁኔታዎች መመልከት የሚቻል ሲሆን፣ በመንገዱ ዳር ያሉት ካሜራዎች መካከልም በፍጥነት መቀያየር ይቻላል።