የVirginia የመኖሪያ ቤቶች እና የማኅበረሰብ ልማት መምሪያ (DHCD) በስቴት፣ በፌደራል እና በአካባቢ መስተዳድር ደረጃ ከሚገኙ የመኖሪያ ቤት አቅርቦት እና የማኅበረሰብ እና ኢኮኖሚ ልማት ተነሳሽነቶች ጋር በአጋርነት ይሠራል። DHCD ፕሮግራሞች በመላው ኮመንዌልዝ የሚገኙ ማኅበረሰቦችን ድምቀት ለመጠበቅ ተግቶ የሚሠራ ሲሆን፣ ይህም ሁለንተናዊ የብሮድባንድ ተደራሽነት ማቅረብ፣ በኢኮኖሚያዊ ልማት ተነሳኘሽነቶች መሳተፍ፣ ስቴት አቀፍ የህንፃ እና የእሳት አደጋ ደንቦችን ማስፈጸም፣ የVirginiaን መኖሪያ ቤቶች እና ህንፃዎች ዋጋ ተመጣጣኝነት እና ውጤታማነት ማስቀጠል፣ መኖሪያ ቤት አልባነትን መፍታት፣ በመላው ስቴት ከመኖሪያ ቤት የሚባረሩ ሰዎችን ቁጥር መቀነስ እና ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸው መኖሪያ ቤቶች ለመገንባት የፈጠራ መፍትሄዎች ማዳበርን ያካትታል። DHCD $2 ቢሊዮን ከሚሆኑት የፌደራል ማገገሚያ ፕሮግራሞች በተጨማሪ $350 ኢንቬስት በማድረግ Virginia ውስጥ ለመኖር፣ ለመሥራት እና ለመነገድ ደኅንነታቸው የተጠበቀ፣ ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸው እና የበለጸጉ ማኅበረሰቦችን ለመፍጠር የVirginia ማኅበረሰቦች አጋር በመሆን ያገለግላል።
600 East Main Street, Suite 300
Richmond, VA 23219
ለአቅጣጫዎች